
Hawassa St. Gabriel Health Team
Sport Health Team
የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ጤና ቡድን እንደ ኢትዮጵያውያን ዘመን አቆጣጠር በ2010 ዓ.ም በ26 አባላት ሲመሰረት ስያሜውንም የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ት/ቤት ጤና ስፖርት ቡድን በማለት ከከተማው የወጣቶች ባህልና ስፖርት ተቋም የህጋዊ ሰውነት ዕውቅና ተቀብሏል፡፡
በአሁን ሰዓት ቡድኑ 40 የሚሆኑ አባላትን በመያዝ፣ የራሱን መተዳደሪያ ደንብ በመቅረጽ፤ ከተማ ውስጥ ከሚገኙ ሌሎች አቻ የጤና ቡድኖች ጋር ተፎካካሪ ለመሆን ጠንክሮ በመስራት ላይ የሚገኝ ቡድን ነው፡፡
የቡድኑ አባላት እንዲኖራቸው የሚጠበቀው
- ጤናማ አካል
- ጤናማ አስተሳሰብ
- መቻቻል
- መረዳዳት
- ተፎካካሪነት
- መከባበር